top of page

ከዚህ ይጫኑ

ሄኖክ ኢትዮጵያዊ - ኤርትራዊ

እውቀት እና ሥልጣኔ፥ ማንነት እና ድኅነት

መግቢያ

ስለ ምድራዊ እውቀት አመጣጥና አካሄድ ስናስተውል፥

ባንድ በኩል ምድራዊ ሕይወታችንን ሲያሻሽል፥

በሌላም በኩል መንፈሳዊ ሕይወታችንን ሲያጣጥል፥

ሙሉ ሆኖ የተፈጠረን ሰው እንዲህ ከሁለት ሲከፍል፥

ምድራዊ እውቀት እና የዘመኑ ሥልጣኔም ትርጉም ያጣል።

የሰው ኑሮ ከራሱ በመነጨ እውቀቱ እንዳይሆን፥ 

በራሱ ካገኘው እውቀት ውስጥ ጣልቃ የገባውን፥

ተፈጥሮአዊ ማንነቱን የወሰደበትን - ወይንም አደናብሮ የቀየረበትን፥

እስቲ እንመልከተው፥ የሰውን ምድራዊ እውቀቱን፥

ከጥንት ከአመጣጡ ጀምረን፤

ከጻዲቁ ሄኖክ መልእክትና አቤቱታ ተነስተን።[1]

እንዲሁም እንመርምር ታሪካዊ ሂደቱን፤

እውቀታችን በኛነታችን ላይ ያስከተለውን - ተፅንኦውን።

በመጨረሻም፥ ኃይልና ሥልጣን፥ የእግዚአብሔር መሆኑን አውቀን፥

ድኅነት የሚገኝ ከእርሱ መሆኑን አምነን፥

ፍቅር፥ ሰላም፥ ጤንነትና ደስታን እንማጸናለን።

 

 

 

[1] “አቤቱ ረድኤቴ መድኃኒቴም፥ የአፌ ቃልና የልቤ ሃሳብ በፊትህ ያማረ ይሁን።” መዝ. 18 (19)፡ 14

 

ሁሉንም ለማግኘት ከዚህ ይጫኑ

Here is one Amharic poem for you, concerning our knowledge and our civilization, its impact on our identity, and more on our spirituality. Enjoy reading it.  There is a lot to learn from it, but remember this -
 
"But the wisdom that comes from heaven is first of all pure; then peace loving, considerate, submissive, full of mercy and good fruit, impartial and sincere" James: 3: 17.
 
"ላኛይቱ ጥበብ ግን በመጀመሪያ ንጽሕት ናት፤ በኁኣላም ታራቂና ገር፥ እሺ ባይ፥ ምሕረትና በጎ ፍሬ የሞላባት፥ ጥርጥርና ግብዝነት የሌለባት ናት።" ያዕ. 3፡17
  • Facebook App Icon
  • Twitter App Icon
  • Wix Google+ page

Copyright © 2018, M.H.Meskale, All rights reserved/ የኮፒ ራይት መብት በሕግ የተጠበቀ ነው።

bottom of page